Svoboda | Graniru | BBC Russia | Golosameriki | Facebook

በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኬኔዲ የሰሜን ሸዋና የደቡብ ወሎ ዘገባዎች

ጋሸና ላይ በህወሓት ታጣቂዎች ሲቪሎች መገደላቸውን አስተዳደሩ ገለፀ

ጋሸና ከጦርነቱ በኋላ
ጋሸና ከጦርነቱ በኋላ

በጋሸና ከተማና በዙሪያዋ 280 የሚሆኑ ሲቪሎች በህወሓት ታጣቂዎች መገደላቸውን የጋሸና ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። ከተማዪቱ ውስጥ የሚገኙ 13 ተቋማት መውደማቸውንም የከተማው ከንቲባ አቶ ሞላ ፀጋው ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።

ጋሸና ላይ በህወሓት ታጣቂዎች ሲቪሎች መገደላቸውን አስተዳደሩ ገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:16 0:00

ህወሓት ግን መሰል ክሶችን ሲያስተባብል ይደመጣል።

ሪፖርተራችን ወደ አካባቢው ሄዶ የጋሸና ነዋሪዎችን አነጋግሯል።

ዝርዝሩ ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ።

ጋሸና ላይ በህወሓት ታጣቂዎች ሲቪሎች መገደላቸውን አስተዳደሩ ገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:50 0:00


ወሎ ዩኒቨርሲቲ ስለደረሰበት ጉዳት

በጦርነቱ ጉዳት የደረሰበት የወሎ ዩኒቨርስቲ ከፊል ገፅታ
በጦርነቱ ጉዳት የደረሰበት የወሎ ዩኒቨርስቲ ከፊል ገፅታ

የህወሓት ታጣቂዎች በወሎ ዩኒቨርሲቲ ላይ አደረሱ የተባለው ጉዳት 15 ቢሊዮን ብር እንደሚገመት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ገልፀዋል።

ፕሬዚደንቱ በአካባቢው ጦርነት ባልነበረበት ወቅት ተዋጊዎቹ ዩኒቨርሲቲው ላይ ከባድ መሣሪያዎችን እንደተኮሱና በወቅቱ እርሳቸውም ቢሯቸው ውስጥ እንደነበሩ ተናግረዋል።

በመቀጠልም የዩኒቨርሲቲውን በርካታ ቁሳቁስና ንብረት ዘርፈው መወሰዳቸውንም የገለፁ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪዎችም ይህንኑ መስክረዋል።

ትግራይ ክልልን በማስተዳደር ላይ የሚገኙት ባለሥልጣናትና የህወሓት መሪዎች ለዚህ ክስ በቀጥታ ምላሽ ባይሰጡም ከዚህ ቀደም መሰል ክሦችን ሲያስተባብሉ መቆየታቸው ይታወቃል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያገኛሉ።

ወሎ ዩኒቨርሲቲ ስለደረሰበት ጉዳት
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:14 0:00


ሸዋሮቢት ውስጥ ተፈፅመዋል ስለተባሉ የመብቶች ጥሰቶች

ሸዋሮቢት ውስጥ ተፈፅመዋል ስለተባሉ የመብቶች ጥሰቶች
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:08 0:00

የህወሓት ታጣቂዎች ሸዋሮቢት ውስጥ በቆዩባቸው ጥቂት ቀናት ፈፅመዋቸዋል ከተባሉ የመብቶች ረገጣ አድራጎቶች ውስጥ በወል እስከመድፈር የሚደርሱ ጥቃቶች ይገኛሉ።

ህወሓት እንዲህ ዓይነት አድራጎቶች በተዋጊዎቹ መፈፀማቸውን በተደጋጋሚ አስተባብሏል።

ሰሞኑን ወደ ሸዋሮቢት ተጉዞ የነበረው ኬኔዲ አባተ

“ሁከት ተፈፅሞናል፤ በሦስት እና በአራት የህወሓት ታጣቂዎች ተደፍረናል” ካሉ የከተማዪቱ ሴቶች ጋር ያደረገውን ውይይት ያካተተ ዘገባ ይዘናል።

ሃይቅ ውስጥ “በትንሹ 48 ሲቪሎች ተገድለዋል” - አስተዳደሩ

ሃይቅ ውስጥ “በትንሹ 48 ሲቪሎች ተገድለዋል” - አስተዳደሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:40 0:00

ሐይቅ ከተማ ውስጥ “በትንሹ 48 ሲቪሎች በህወሓት ታጣቂዎች ተገድለዋል” ሲል የከተማ አስተዳደሩ ክሥ አሰምቷል።

በከተማዪቱ ውስጥ የአዕምሮ ጤና ችግር የነበረባቸው ጭምር የጥቃት ዒላማ መሆናቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ሃሳባቸውን ያካፈሉ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ ታጣቂዎቻቸው በሲቪሎችና ሲቪል ተቋማት ላይ ጥቃት እንደማይፈፅሙ የሚናገሩት የህወሓት መሪዎች በቅርቡ ባወጡት መግለጫ ጭምር ተመሳሳይ ክሦችን ያስተባብላሉ።

ሐይቅ ከተማና ጉዳቷ

ሐይቅ ከተማ
ሐይቅ ከተማ

ሐይቅ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ማኅበራዊ አገልግሎት ሰጭና የመንግሥት ተቋማት በሙሉ በህወሓት ጉዳት እንደደረሰባቸው የከተማ አስተዳደሩ ተናግሯል።

በአሁኑ ወቅት ለሰዉ አገልግሎት መስጠት የሚችል ተቋም እንደሌለ የከተማዪቱ ምክትል ከንቲባ መሱድ አበራ ገልጸዋል።

ጉዳት ከደረሰባቸው ተቋማት አንዱ ከሆነው ሐይቅ ሆስፒታል “የህወሓት ታጣቂዎች መድኃኒቶችንና የህክምና መሣሪያዎችን ጨምሮ የሆስፒታሉን ንብረቶች ዘርፈው ሲወስዱ ማየታቸውን” አንድ የሆስፒታሉ ሃኪም ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችንና የተቋማት ውድመቶችን በተመለከተ የሚቀርቡባቸውን ክሦች፣ የህወሓት መሪዎች በተደጋጋሚ አስተባብለዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ።

ሐይቅ ከተማና ጉዳቷ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:18 0:00


ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG