Svoboda | Graniru | BBC Russia | Golosameriki | Facebook

በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሞዛምቢክ የጀልባ አደጋ 96 ሰዎች ሞቱ


ሞዛምቢክ ሰሜናዊ የባህር ዳርቻ
ሞዛምቢክ ሰሜናዊ የባህር ዳርቻ

እንደነገሩ በተሠራ ጀልባ ላይ ሆነው ሲጓዙ የነበሩ 96 ሰዎች መሞታቸውንና 20 የሚሆኑት ደግሞ የደረሱበት እንደማይታወቅ የሞዛምቢክ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

ጀልባዋ የሰመጠችው በሃገሪቱ ሰሜናዊ የባሕር ዳርቻ ትናንት እሁድ እንደነበር ታውቋል።

ጀልባዋ ቀድሞ ለዓሣ ማስገሪያነት የተሠራችና በኋላ ወደ መጓጓዣነት እንደተቀየረች እንዲሁም ከአቅሟ በላይ ተጭና እንደነበረ የአካባቢው ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

አንዳንዶቹ ተጓዦች በዩኔስኮ ቅርስነት በተመዝገበችው ሞዛምቢክ ደሴት ላይ ለሚደረግ ትርዒት በመጓዝ ላይ የነበሩ ሲሆን፣ ሌሎቹ ደግሞ በሃገሪቱ የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ሽሽት ላይ እንደነበሩ ተግሯል።

በዓለም ካሉ እጅግ ደሃ ሃገራት አንዷ በሆነችው ሞዛምቢክ፣ 15ሺሕ ሰዎች በኮሌራ እንደተያዙ ሲታወቅ፣ ካለፈው ጥቅምት ወዲህ 32 ሰዎች በበሽታው ሕይወታቸውን አጥተዋል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG