Svoboda | Graniru | BBC Russia | Golosameriki | Facebook

በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ: የሰላም መንገዶች - አንድ ዓመት ከፕሪቶሪይያ ወዲህ

ኢትዮጵያ: የሰላም መንገዶች - አንድ ዓመት ከፕሪቶሪይያ ወዲህ

የአሜሪካ ድምፅ የአፍሪካ ቀንድ አገልግሎት፣ “ኢትዮጵያ: የሰላም መንገዶች - አንድ ዓመት ከፕሪቶሪይያ ወዲህ” በሚል ርእስ፣ የአንድ ሰዓት ተኩል ልዩ የቴሌቪዥን ውይይት ውይይት አዘጋጅቷል።

ውይይቱ፣ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል፣ ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ-ፕሪቶርያ ላይ የተፈረመው “ግጭትን በዘላቂነት የማቆም የሰላም ስምምነት” አፈጻጸም በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? ከዘላቂ ሰላም፣ ከተጠያቂነት፣ ከዴሞክራሲ እና ከሰብአዊ መብቶች አያያዝስ አንጻር ምን ውጤት አመጣ? የሚሉትንና ሌሎችንም ጥያቄ ያነሣል።

በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ስቱድዮ በተካሔደው በዚኽ ውይይት፣ የተለያዩ ሐሳቦች ያሏቸው ትውልደ ኢትዮጵያን ተገኝተው ሐሳባቸውን አንሸራሽረዋል።

የስቱዲዮ ተወያይ እንግዶች የነበሩት፡-

  • አቶ ጌታቸው ተማረ፥ የሕግ ባለሞያ እና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ናቸው።
  • መዓዛ መሐመድ፥ የሮሃ ቴቪ ተባባሪ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ፣ እንዲሁም የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ናቸው። የአሜሪካ መንግሥት በየዓመቱ የሚሰጠው የዓለም አቀፍ ጽኑ ሴቶች ሽልማት የዘንድሮ ተሸላሚም ናቸው።
  • ዶክተር ኄኖክ ጋቢሳ፣ ዓለም አቀፍ ሕግንና ሰብአዊ መብቶችን ያጠኑ የሕግ ባለሞያ ናቸው። በዓለም አቀፍ የኦሮሞ የሕግ ባለሞያዎች ማኅበርም ተባባሪ ሊቀ መንበር ኾነው ያገለግላሉ።

በስካይፕ መሥመራችን ላይ የተገኙ ተወያዮች የነበሩት፡-

  • አቶ ሰዒድ ቦሩ፥ በኦሃዮ ግዛት ነዋሪ ናቸው። በአሜሪካ የሚኖሩ የአፋር ተወላጆች ማኅበር ሊቀ መንበርም ናቸው።
  • አቶ ኢሳይያስ ኀይለ ማርያም፥ የሕግ ባለሞያ ናቸው። “የፕሪቶርያ ስምምነት በተለይ ለትግራይ ሕዝብ ምን አመጣ?” በሚል የግምገማ ጹሑፍ አሳትመዋል።
  • አቶ ልደቱ አያሌው፥ በኢትዮጵያ ፖለቲካ የሰላማዊ ትግል ስልት ሳያሰልሱ በግንባር ቀደምነት በመሳተፍ ጉልሕ ተሳትፎ ያላቸው ታዋቂ ፖለቲከኛ ናቸው። በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምሥረታ እና አመራርነትም ይታወቃሉ። አኹን በዩናይትድ ስቴትስ፣ አትላንታ ግዛት ውስጥ ይኖራሉ።
  • ረዳት ፕሮፌሰር ጉባኤ ጉንዳርታ፥ በፍሎሪዳ ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ መምህር ናቸው።

XS
SM
MD
LG