Svoboda | Graniru | BBC Russia | Golosameriki | Facebook

በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

ዓርብ 26 ኤፕሪል 2024

Calendar
ኤፕሪል 2024
እሑድ ሰኞ ማክሰ ረቡዕ ሐሙስ ዓርብ ቅዳሜ
31 1 2 3 4 5 6
7 8 9 10 11 12 13
14 15 16 17 18 19 20
21 22 23 24 25 26 27
28 29 30 1 2 3 4
ፎቶ ፋይል፦ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ፎቶ ፋይል፦ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በግጭት ለምትታመሰው፣ በጎርፍ እና ድርቅ ለተጠቃችው ኢትዮጵያ የሚያስፈልገውን የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦት ከፍ ለማድረግ 1 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ማቀዱን ዛሬ ማክሰኞ አስታወቀ።

ከኢትዮጵያ እና ከእንግሊዝ መንግሥታት ጋራ በመተባበር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጄኔቫ ላይ ያካሄደው የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ ለ15.5 ሚሊዮን ሰዎች የሚሆን የነብስ አድን ርዳታ እና ለተጨማሪ 10 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሰዎች የሚሰጠውን የምግብ ዕርዳታ መጠን ለማሳደግ የታለመ መሆኑ ተመልክቷል።

“የአስቸኳይ ርዳታ የሚጠይቁት ሁኔታዎች በድርቅ እና በጎርፍ እንዲሁም በግጭት እየተባባሱ የመጡ ናቸው” ሲል ተመድ አስታውቋል።

"ኤልኒኞ በሰሜናዊ የሃገሪቱ ክፍል በሚገኙ ደጋማ አካባቢዎች ያለውን ድርቅ በማባባሱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የውሃ አቅርቦት ዕጥረት፤ የግጦሽ ሳር እጦት እና የምርት መጠን ማሽቆልቆል ያስከተሏቸውን ፈተናዎች ለመቋቋም እየተጣጣሩ ነው" ብሏል።

በዚህ ዓመት በግጭቶች እና የአየር ንብረት ለውጥ ባስከተሏቸው ችግሮች የተነሳ ቁጥራቸው ከ21 ሚሊየን በላይ የሚደርሱ ሰዎች በኢትዮጵያ ሰብአዊ ርዳታ እንደሚፈልጉ የገለጸው ኦቻ፣ ከሐምሌ እስከ መስከረም ባሉት ወራት ቁጥራቸው 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን የሚደርስ ሰዎች ለከፋ የምግብ ዋስትና ዕጥረት መጋለጣቸውንም ገልጿል።

በተያያዘ እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ርዳታ መጠን ለማሳደግ ተጨማሪ 100 ሚሊዮን ፓውንድ (124 ነጥብ 58 ሚሊዮን ዶላር) እንደምትሰጥ አስታውቃለች።

በብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የልማት እና የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ሚኒስትር አንድሪው ሚሸል ሲናገሩ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ርዳታ ለመስጠት የተገባው ቃል የባህረ ሰላጤውን አገሮች ጨምሮ “ሌሎች ሃገራት እንዲሳተፉ ያበረታታል” የሚል እምነት እንዳደረባቸው ተናግረዋል።

 የማላዊው ገበሬ በበቆሎ ማሳቸው ውስጥ ሲዘዋወሩ ዋና ከተማዋ አካባቢ ሊሎንግዌ፣ ማላዊ
የማላዊው ገበሬ በበቆሎ ማሳቸው ውስጥ ሲዘዋወሩ ዋና ከተማዋ አካባቢ ሊሎንግዌ፣ ማላዊ

በተፈጥሮ የሚከሰተው ኤልኒኞ፣ በፓስፊክ ምሥራቃዊ ውቅያኖስ አካባቢ ከሚታየው ያልተለመደ የውሃ ግለት የሚነሳው ሙቅ አየር በዓለም ዙሪያ የአማካይ ሙቀት መጠን እንዲጨምር በማድረጉ እና እንዲሁም ወደ ከባቢ ዓየር የሚለቀቀው በካይ የካርቦን መጠን የከሰቷቸው ሁኔታዎች ተደራርበው ድፍን ደቡባዊ አፍሪቃ ባለፉት ዓመታት አጋጥሞት በማያውቅ አስከፊ ድርቅ እየተናጠ ይገኛል። ይህንንም ተከትሎ ማላዊ፣ ዝምባብዌ እና ዛምቢያ ባለፈው ወር አከባቢውን በመታው ድርቅ ሳቢያ የአስቸኳይ ጊዜ አውጀዋል።

የምግብ አቅርቦት ምንጮች እየነጠፉ ባሉባት ማላዊ፡ የማሳ ሰብል ስርቆት ብርቱ ችግር እየሆነ ነው። የበቆሎ አምራች የነበሩ ኡላሊያ ላፑሶኒ የተባሉ አንዲት ገበሬ ሲናገሩ፡ በድርቁ ሳቢያ የዘሩት በቆሎ ባለማፍራቱ በአሁኑ ወቅት የረሃብ አደጋ ተጋርጦባቸዋል።

"እስኪ አስቡት ለዚህ ወር የሚሆን ምግብ የለንም፤ እንዴ አድርገን ተርፈን እስከሚቀጥለው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ መድረስ እንችላለን? ከባድ ነው የሚሆነው” ብለዋል የደረቀ ማሳቸውን እያሳዩ።

ከዚሁ በተያያዘም፡ የማላዊው ፕሬዝዳንት ላዛረስ ቻክዌራ ሃገራቸውን ከረሃብ አደጋ ለመታደግ አለም አቀፍ ለጋሾች እጃቸውን እንዲዘረጉ ጠይቀዋል። በዓለም ዙሪያ በ2023 አዲስ ሪከርድ ያስመዘገበው የአየር ንብረት ለውጥ ኤልኒኞ የሚያሳድረውን ተፅእኖ ማባባሱም ተዘግቧል።

ዓለም አቀፉ የረድኤት ድርጅት ኦክስፋም ባለፈው ሳምንት እንዳስጠነቀቀው፡ በደቡባዊ አፍሪቃ ከ24 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በድርቅ ሳቢያ ለረሃብ፣ የተመጣጠነ ምግብ እና የውሃ እጥረ ተጋልጠዋል።

በማላዊ በተከሰተው ድርቅ ሳቢያም ‘ዘጠኝ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ተጎድተዋል’ ሲል ዩኒሴፍ አስታውቋል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG